ነፍጠኝነትን የግል ርስት አድርጎ የነፍጠኛ ሥርዓት ባላደራና ጠባቂ መሆን: ከነፍጠኝነት የባሰ አሳፋሪ አረመኔያዊ (savage) ተግባር ነው!

 

ነፍጠኝነትን የግል ርስት አድርጎ የነፍጠኛ ሥርዓት ባላደራና ጠባቂ  መሆን፣ ከነፍጠኝነት የባሰ አሳፋሪ  አረመኔያዊ (savage) ተግባር ነው!

በ Dr. Tsegaye Ararssa

📌📌📌📌📌

ነፍጠኛና ነፍጠኝነት ሲወቀስ አንተን ብቻ በተለይ የሚቆጠቁጥህ ከሆነ: ወይ እራስህ "ዘመናዊ" ነፍጠኛ ነህ: ወይ የነፍጠኛ(-ገባር) ሥርዓትን መልሰህ ለማቆም የምትተጋ  ቀልባሽ (reactionary) የፖለቲካ ኃይል ነህ:: 

ትምክህተኛ ሲኮነን አንተን ብቻ በተለየ ሁኔታ የሚያንገበግብህ  ከሆነም: በተመሳሳይ መልኩ : ወይ የአንድ ቡድንን የበላይነት የምታቀነቅን ትምክህተኛ (chauvinist) ነህ: ወይም በትምክህት ላይ የተመሠረተ ሥርዓትና አገረ-መንግሥት ለማቆም የምትተጋ የሕዝቦች እኩልነትና ወንድማማችነት ጠላት ነህ:: 

እነነውር ጌጡ: ነፍጠኛነትን ለፍትህ ከሚታገሉ ተራማጅ ኃይሎች ሁሉ ጋር በአንድነት ሁነው በመኮነን አሰላለፋቸውን ከዘመኑ ጋር ከማስተካከል ይልቅ: የነፍጠኛነት ጠበቃ ሆነው: አለፍ ሲልም "ነፍጠኛ ነኝ" የሚል ጽሑፍ የተከተበበት ልብስ ለብሰው በትውልዱ ላይ ይፎክራሉ::

ይሄም ሳያንስ: "ለምን ቃሉን ታነሳሳላችሁ? ቃሉን መጠቀምም የጥላቻ ንግግር ነው" ሊሉ ይቃጣቸዋል::  

ሥርዓቱ: ተግባሩና በሕዝቦች ላይ ያደረሰው መጥነ-ሰፊ ጥፋት ሳያስቆጣቸው: ቃሉን አንስተን ሥርዓቱንና ተግባሩን መኮነናችን ያስቆጣቸዋል::

ክፋትን አትኮንኑ ወይም አወድሱልን ሊሉን ይፈልጋሉ:: 

ክፋትን አለመኮነን: ክፉ ተግባሩንና ውጤቱን እንደ በጎነት ተቀብሎ ማጽደቅ ነው:: ከክፋት ተግባሩ ፈፃሚዎች ጋር መተባበር ነው:: ይሄ ደግሞ ግፍ ከመፈጸም አልፎ የግፍ ተጠቂዎችን ፍትህ መቅበር ነው:: ሁለት በደል ነው:: አንድእኛ: በህዝብ ላይ ግፍና ኢፍትሃዊነትን መፈጸም ነው:: ሁለተኛ: የግፍ ታሪክንና ሃቅን: እንዲሁም የተጠቂዎችን የተኖረ መከራ (ትውስታቸውንና ትዝታቸውን) መቅበር ማዳፈን ወይም መሰረዝ ነው:: አረመኔነት (savagery) ነው::

ከሁሉም በላይ ደግሞ: ዛሬ: በዚህ ባሁኑ ዘመን: ያንኑ ግፍ ለመድግም በትውልዱ ላይ መዛትና ለማስፈራራት  መሞከር ነው:: የጥላቻና የሽብር ንግግርን መንዛት ነው:: ለግፈኞች ተቆርቁሮ: ተጠቂዎችን (ወይም ትሩፋኑን) እውነታቸውን እንዳይናገሩ ማሸማቀቅ ነው:: አሸማቃቂዎቹም የነፍጠኛው ሥርዓት ወራሽ: ባላደራና: አራማጅ (undertaker) መሆናቸውን በይፋ ማረጋገጥ ነው::

አንተን የነፍጠኝነትና የትምክህተኝነት ጠበቃ መሆንህ ሳያሳፍርህ: እኔ የነፍጠኝነትን ክፋት: ያስከተለውንና ዛሬም እያስከተለ ያለውን የግፍ ክምር መውቀሴ በምን ሂሳብ:ለምንና እንዴት ያሳፍረኛል: ያስወቅሰኛል?

ግፍ ባትፈሩ: ነውርን መፍራት ነበረባችሁ:: በነውር ማጌጣችሁ ሳያንስ: የነውራችሁን ነውርነት መግለፅ የጥላቻ ንግግር ነው ስትሉ:  ጥላቻችሁ ምንኛ እንዳሳወራችሁ አጋለጣችሁ::

አዎን: ደግሜ እላለሁ:: ነፍጠኝነት ወንጀል ነው:: ወሮ-በላነት ነው:: ነፍጠኝነት ጦረኝነት ነው:: ወራሪ-ነጣቂነት ነው:: እንደ lynching ያለ የጥላቻ ፍጅት ተግባር ነው:: በታሪክም ቢሆን: የነፍጠኛ-ገባር ሥርዓት: ዓላማውም ውጤቱም: ዘራፊ-ቀማኛነት: አሸባሪ-ገዳይነት: ዘር-አጥፊ ወንጀለኝነት ነው::


("ነፍጠኝነትን የኛ (የብቻችን ርስት) ነው: ነፍጠኞች እኛ ነን: ነፍጠኛን መጥላት እኛን መጥላት ነው: ነፍጠኛን መኮነን እኛን መኮነን ነው" ለሚሉ: ነውርን እንደጌጥ ለሚሻሙና ነውራችንን አወድሱ-መርቁልን ለሚሉ ተላላዎች የተፃፈ::)

📌📌📌📌📌

Comments

Popular posts from this blog

A Response to Lifetime President of Eritrea Isaias Afewerki's Remarks on Oromummaa

Oromo Nationalism and the Ethiopian Discourse: Between Misrepresentation and Democratic Aspiration